የመሬት ይዞታ መብት በኃላፊነት ማስተዳደርን የተመለከተ የኢንቬስተሮች ሙያዊ መምሪያ
በግብርና ስራ ላይ የሚውል ኢንቨስትመንት በምግብ ራስን አለመቻልንና ድህነትን ለመቀነስ እጅጉን አስፈላጊ ነው፡፡ ከ2000 ዓ.ም ጀምሮ በታዳጊ አገሮች ውስጥ የእርሻ ቦታ ተፈላጊነት በከፍተኛ ደረጃ ጨምሯል፡፡ በዚህ አኳያ መሬት አጉዋጊ መስህብነት ያለው ቋሚ ንብረት ተደርጐ ይወሰዳል፡፡ በማህበራዊ ዘርፍ ረገድ በመሬት ላይ የሚደረጉ ኢንቨስትመንቶች ቅይጥ ውጤቶችን አምጥተዋል፡፡ እንደነዚህ ያሉ ኢንቨስትመንቶች የአንዱን አካባቢ ማህበረሰቦች ተጠቃሚ የማድረግ አቅም አላቸው፡፡ ይህም አነስተኛ አቅም ያላቸው ገበሬዎች የካፒታል፡ የቴክኖሎጂ፣ የእውቀትና የግብይት ቦታዎች አቅራቦት እንዲኖራቸው በማድረግ ነው፡፡ ከዚሁ ጐን ለጐን የላቀ ኢኮኖሚያዊ እምርታ እና የግብርና ምርታማነትን የመሳሰሉ ጠቀሜታዎችን ማግኘት ያስችላሉ፡፡ ቢሆንም እነዚህ ኘሮጅክቶች ብዙ ግዜ የአካባቢውን ነዋሪዎች መብቶቻቸውን እንዲያጡና መሬታቸውንና በመሰል የተፈጥሮ ሃብቶችም መ ጠቀም እ ንዳይችሉ በ ማድረግ ለ ተጐጂነት ይ ዳርጉዋቸዋል፡፡ እ ንደዚሁም በ ምግብ ዋስትናና በገጠር ነ